torsdag 26. desember 2013

ሽብርተኛ ነገር ነህ!!! ምን??? ሰምተሃል!!!

መለሰ ድርብሣ
ማታ እኛ ግቢ መብራት ጠፍቶ ከቴሌቭዥኑ ሶኬት ሳናለያይ ተኛንና ገና ሳይነጋ መብራቱ ስመጣ በመኝታ ክፍሌ ውስጥ ያለው ቴሌቭዥን ድንገት ስጮህ አሸበረኝና ሽብርተኛ!!! አልኩት፡፡ ለምን እንደሆነ ተውቃላችሁ? ሽብርተኛንና ሽብርን በጣም ስለሚጠለ ብቻ ነው፡፡ ከጀመርን አይቀር ስለ ሽብርተኛና ሽብር ትንሽ እናውጋ እስቲ፡፡
ወደ “ነገር ግንና ጥርጣሬዎቼ” እመለሳለሁ፡፡ መጀመሪያ ወደማያወላውልና መቼም ቢሆን ወደማይዛነፍ ሽብርተኝነት ላይ ያለኝ አቋም ቀጥታ ልዝለቅ፡፡ መቼም ቢሆን በምንም ሁኔታ አቋሜ ልቀየርም ሆነ ልከለስ አይችልም፡፡ በማንም ይሁን በማን በንፁሃን ላይ የሚደርስ ጥቃት አምርሬ ነው የምቃወመው፡፡ እንኳን ቦምብ ቀርቶ ጥፊ እንኳ ያንገበግበኛል፡፡ ችግር ኣለ የሚል አካል በሰላማዊ መንገድ መታገል አይሆንም ካለ ደግሞ ከሚመለከተው ጋር ጦር ተማዞ መተጋተግ እንጂ የምን በቀን አንዴ እንኳ መብላት የማይችል ምስኪን ላይ ጡንቻ ማሳየት ነው!!!? የምን የማይመለከተውን ተራ ሰው ማሸበርና ኢላማ ማድረግ ነው!!!? እናም ሽብርተኝነት ላይ ያለኝ አቋም የማያወላዳ ግልጽና ግልጽ ቀጥተኛ ነው፡፡ ይልቁንስ ነገር ሳላበዛ ወደ “ነገር ግንና ጥርጣሬዬ” ልመለስ እስቲ…
አንደኛው ነገር ሽብርተኛ ማን ነው??? እኔ እስከምገባኝ ድረስ ዜጎች ላይ ሽብርን የሚፈጥርና የራሱን ጥቅም ለማስከበር ስባል በንፁሃን ላይ የሞትና የማሰቃየት አደጋ የሚያደርስ ማንም ቢሆን ማን ሽብርተኛ ነው፡፡ ለአንደፍታ አንድ ነገር አስቡ እስቲ….በቁጥር ደረጀ ብሎም በደረሰው ጉዳት አንፃር እንኳ ብመዘን ቀጥታ የተፈፀመው የሽብር ድርጊት ነው ወይስ ለፖሊትካ ፍጆታና የፖሊትካን ጥቅም ለማስከበር እንድሁም ጎልተው የሚሰሙ ድምፆችን ለማፈን ስባል በስውር የሚፈፀም ስንትና ስንት ነገር ነው ሚዛን ልደፋና ትልቅ አጀንዳ ልሆን የሚችለው? ሽብርተኝነት ስጋት አይደለም ማለቴ ሳይሆን ሌሎች ሽብርተኝነት ያልተባሉ ግን የማይተናነሱ ነገሮችም ልታዩ ይገባል!!! ደርግም እኮ ለራሱ እየጨፈጨፈ ሌሎችን ወንበዴ ሲል ነበር….
ሁለተኛ ነገር ደግሞ ፖሊትከኞችን የስፖርት ቃል ልጠቀምና ማኖ ለማስነካት በመጣጣር ለራስ በማኖ ውስጥ ተጨመላልቆ ይልቁንም ማኖ ማስነካቱ ቀርቶ በቅጣት ምት በራስ ላይ እንድቆጠር በር መክፈት ዕውቀት-አጠር ያሰኛል፡፡ ሰዎች!!! ፖሊትካውን በዕውቀት እነድርገው እንጂ…በእርግጥ የተሰማንን መናገር ይቻላል፡፡ ግን መናገርና ትንታኔ መስጠት ለየቅል ነው፡፡ የዓረፍተነገሮች እንድምታ እንኳ በደምብ ሳያገናዝቡ በፖሊትካ ውስጥ ዘብ ለመቆም መጣጣር ከጫወታ ውጪ ሆኖ ኳሷን ለማስቆጠር እንደመጣር ነው፡፡ ይሂን ያልኩበት ያለምክንያት አይደለም፡፡
በተደጋጋሚ አንድ ነገር በሚዲያ ላይ ስሰማ አንድ ጊዜ እንኳ ብሸወዱ ሁለተኛውና ከዛ ኋላ መባነን የለም እንዴ አልኩኝ፡፡ ፕሮፌሰር መረራ ጉድና ስለቦሌ የቦምብ ፍንዳታ ተጠየቁና የመንግስት ድራማ ልሆን ይችላል ብለው መለሱ፡፡ ፕሮፌሰሩን ማኖ ለማስነካት ሲባል በሚዲያ ተደጋገመ፡፡ ነገር ግን ፕሮፌሰሩ የተናገሩትን በደምብ ያለመገንዘብና እንድምታውን ያለማጤን ነው እንጂ ማኖ ለማስነካት ተብሎ ማኖ ባልተነካ ነበር፡፡ የፕሮፌሰሩ ንግግር ፍሬሀሳብ እኮ መንግስትም ከዚህ ያልተናነሰና እንደዚህ ዓይነቱን ድርጊት ለፖሊትካ ፍጆታ ይፈፅማል ነው፡፡ ድሮም ሰዉ በጥርጣሬ ነገሮችን ስለሚመለከት ይሄን ደግሞ ደጋግሞ ሚዲያ ላይ መልቀቅ ፕሮፌሰሩን ማኖ በማስነካት ለመንግስት ዘብ መቆም ሳይሆን በመንግስት ግብ ላይ ማስቆጠር ብሎም የህዝቡን ጥርጣሬ ማስፋት ነው፡፡ ለዚህ ነው የተሰማንን መናገር እንችላለን ግን ያለ ጥልቅ ዕውቀት መተንተኑ ግን መለጠፍና መምረግ ይሆናል ያልኩት፡፡
ስለፖሊትካ ጥልቅ ዕውቀት የሌለው ስለ ፖሊትካ ልተነትን ገብቶ ተተርትሮ በራሱ ግብ ላይ ስያስቆጥር፤ ስለኢኮኖሚው እንድሁ ሁለት አሃዝ ገብቶ ለማደነጋገር መደነጋገር ስይዘው….ያለሙያ መተንተን ትርፉ ዕውቀት-አጠር መባልና በራስ ግብ ላይ ማስቆጠር!!!

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar